Saturday, June 20, 2015

5 ስለ ግብረ-ሶዶማዊነት ("homosexual lifestyle") የተዛቡ ንግግሮች እና እውነታው

ከልጅነቴ ጀምሮ እኚን እና እንደኚ ያሉ ሌሎች ተመሳሳይ ሀሳቦች ስለ ግብረ-ሶዶማዊነት ሲወሩ ሰምቻለው። ግን ከብዙ ጥናት እና የራሴ የኑሮ ልምድ በኋላ እውነታውን ለመረዳት ችያለው። ከነዚህ ሀሳቦች ዋና ዋና ያልኳቸው አምስቱ እኚህ ናቸው። (ጥሩ የአማርኛ ቃል ስላጠረኝ "ተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪ" ለማለት "ግብረ-ሶዶሜያዊ" የሚለውን ቃል ተጠቅሜአለው።)

1 - "ኢሠብዓዊ እና ከተፈጥሮ ውጪ የሆነ ተግባር ነው"

ብዙ ጊዜ ይህን ሃሳብ ለማሳመን አንዳንድ ጥያቄዎቸን ይሰነዝራሉ። "የግብረ-ሥጋ ግኑኝነት ዓላማ ልጅ መውለድ ከሆነ ግብረ-ሶዶማዊያን ለምን ልጅ አይወልዱም?"፣ "ግብረ-ሶዶማዊነት በሰዎች ላይ እንጂ በሌሎች እንስሳት ላይ የት አለ?" ፣ "እንዴት ሊሆን ይችላል?"።
የግብረ-ሥጋ ግንኙነት ዓላማ ልጅ መውለድ አይደለም! ዓላማው ያ ቢሆን ኖሮ በዚ ዓለም ላይ ሚወለዱ ህፃናት ቁጥር  በዚ ዓለም ላይ በወንድ እና በሴት መሃል ከሚደረግ የግብረ-ሥጋ ግንኙነት ቁጥር በላይ ይሆን ነብር፤ እውነታው ግን ያ አይደለም። በርግጥ ልጅ መውለድ የግብረ-ሥጋ ግንኙነት አንድ ውጤት ነው፤ ነገር ግን አንድን ሰው ከ ሌላ ሰው ጋር የግብረ-ሥጋ ግንኙነት ለመፈፀም የሚገፋፋው ዘሩን ተክቶ ለማይት፣ ወልዶ ለመሣም፣ ወይም 'አይኑን በአይኑ ለማየት' ሳይሆን ከውስጥ የሚመነጭ የወሲብ ጥማትን ለማርካት ነው። በኢትዮጲያ ውስጥ ለረጅም ጊዜ የግብረ-ሥጋ ግንኙነት እንደ ነውር እንጂ እንደ የሰው-ተፈጥⶂዊ-ባህሪ ተደርጎ ስለማይታይ ይህን እውነታ ሰዎች አይገነዘቡትም።
ግብረ-ሶዶማዊነት ከሰው ዘር ውጪ በ ሌሎች እንስሳቶች ላይ ይታያል!!!!
ምንም እንኳን የሰው DNA ውስጥ የዛን ሰው ወሲባዊ ፍላጎት(sexual orientation) ሚቆጣጠር GENE ባይኖርም ሌሎች Epigenetic marks በእርግዝና ጊዜ እና ከወሊድ በኋላ የዛ ሰው GENE እንዴት እንደሚሰራ ይቆጣጠራሉ። እኚህ Epigenetic marks በእርግዝና ጊዜ የሆርሞን መጠን መዛባት ምክንያት ይከሰታሉ። በዚህም ምክንያት አንድ ሰው ግብረ-ሶዶማዊ ሆኖ ሊወለድ ይችላል

2 - "በፀሎት እና  በልምምድ ከግብረ-ሶዶማዊነት መላቀቅ ይቻላል"

ይህ እውነት ቢሆን ኖሮ ዛሬ ጌይ ሆኜ ይህንን ስፅፍ አልገኝም ነበር። 10ኛ ክፍል እያለው 'ሮዝ' መጽሄት ስለ 'ግብረ-ሶዶማዊነት' ዘግበው ነበር። በዘገባውም ውስጥ ሌሎች ጌይ የሆኑ ሰዎች ታሪካቸውን በትንሹ አጋርተው ነብር። በዚህም ጊዜ ነው ስለራሴ ማንነት የተገነዘብኩት። ግን ይህ ግንዛቤ ያመራኝ ወደ ጭንቀት እና ፍርሃት ነብር። ታድያ እንደ ማንኛውም ክርስቲያን በፍርሃት ጊዜ ወደ ፈጣር ዞርኩኝ። ፆም ፣ ፀሎት ፣ ስግደት ፣ ጥምቀት ፣ ቅዳሴ ፣ ሰምበት ትምህርት ፤ ምንም ለውጥ። በመጨረሻ ፈጣሪዬ እኔን ከመቀዬሙ የተነሳ ከዚ ህይውት ሊያድነኝም እንኳ ፈቃደኛ ያልሆነ ነበር የመሰለኝ። ህይወቴን ከመጥላቴ የተነሳ ህይውትን ሚያሳምሯት ትናንሽ ደስታዎችን እንኳ መጎንጨት አቃተኝ። ያጋጠመኝን መጥፎ አጋጣሚ ሁሉ 'ከፈጣሪ የወረድ የሚገባኝ ቅጣት ነው' እያልኩ አይምሮዬ ውስጥ በፈጠርኩት ትንሽ ሲዖል ስነድ ነብር። እርግጠነኛ ነኝ እኔ ብቻ አይድለሁም በእንዲህ አይነት አግጣሚ ውስጥ ያለፍኩት። ለዚያውም በቅርብ ማውቀው የነበረ ልጅ እራሱን እጥፍቷል (6ኛ ክፍል ተማሪ ነብር መርዝ ጠትቶ ሲሞት)። በርግጥ ግብረ-ሶዶማዊነት ሐጥያት ነው(በአንዳንድ ሐይማኖቶች መሰረት)፤ ግን ሐጥያት የሌለበት ማን ነው? ሐጥያት የሌለበት ካለ የመጀመሪያውን ስድብ ይሰንዝር!

3 - "ወደ ግብረ-ሶዶማዊነት የገባኸው  . . . . .  ስለሆነ ነው"

አንዳንድ ጊዜ ሰዎች የሚሰጡት መላምት በጣም ያስቃል። "ትንሽ ሆነህ ተደፍረህ ስለነብር ነው"፤ በህይወቴ የወሲብ ጥቃት ደርሶብኝ አይውቅም። አንድ ወንድ (ጌይ ቢሆንም እንኳ) የውሲብ ጥቃት ቢደርስበት፣ ያንን ጥቁር ቀን ስለሚያስታውሰው ወሲብ የተባለ ከነጭራሹ ያስጠላዋል እንጂ የበለጠ እንዲወደው አያደርገውም። "ከእናትህ ጋር ብቻ (ያለ አባት) ስላድግ ነው"፤"ያደግክበት አካባቢ ተሰጠዖ ነው"፤ ለብዙ ጊዜ ይህ እውነት ይመስለኝ ነብር፣ ነገር ግን ይህ እውነት ቢሆን ኖሮ ታናሽ ወንድሜም ጌይ ይሆን ነብር። ሁለታችንም ያለአባት ከአንድ አይነት እናት ጋር፣ አንድ አይነት ትምህርት ቤት ውስጥ፣ እና አንድ አይነት ቤት/ሰፍር ውስጥ አንድ አይነት ምግብ እየበላን ነው ያደግነው ግን እኔ ብቻ ነኝ ግይ። ለምን?  ከሁሉም ሚገርመኝ ግን "ግብረ-ሶዶማዊ የሆንከው አጉል ዘመናዊ ለመሆን ፈልገህ ስለመረጥክ ነው" ሚለው ነው። ምርጫ ቢኖረኝ ኖሮ በብቸኝነት ግራተጋብቶ መሰቃይትን፣ በዘመድ በጎረቤት በወላጅ ... በሐገር መጠላትን፣ በእስር እና በሞት መቀጠታትን (ብዙ አፍሪካዊ አገሮች ውስጥ ግብረ-ሶዶማዊነት በህግ ያስቀጣል) ለምን ብዬ እመርጣለው??  ከላይ እንድጠቀስኩት ግብረ-ሶዶማዊነትን መለውጥ አይቻልም፤ እንደዝያውም ደግሞ አንድ ሰው ጌይ ሆኖ ሳይወለድ ጌይ መሆን አይችልም። ይህንን ማመን ለሚያቅጣቸው መልሴ ቀላል ነው "ለ1 ቀን ጌይ ሁኑ እና ወደነበራችሁበት ተመልሳቹህ አሳዩኝ!"

4 - "ግብረ-ሶዶማዊያን = የወሲብ አጥቂዎች"

ማንኛውም አይነት የወሲብ ጥቃት ሊገፀፅ እና ሊወገድ የሚገባ ተግባር ነው። በተለይም በንፁሃን ህፃናት ለይ የሚፈፀም የወሲብ ጥቃት በጣም አሰቃቂ ነው። በአዲስ አበባ ውስጥ ከሚደርሱት የወሲብ ጥቃቶች ውስጥ 38.5%  ህፃናት ላይ ነው። ከነዚህም ውስጥ 68 % ጥቃቶች የሚደርሱት ህፃናቱ በሚያውቋቸው ሰዎች ሲሆን 29% በህፃናቱ ዘመዶች ነው። እዚህጋ ማለት የፈለጉት ማንኛውም ሰው የወሲብ አጥቂ ወይም ተጠቂ ሊሆን ይችላል። የወሲብ ጥቃት የወሲብ ጥቃት ነው ። አንደኛው ከሌላኛው ሚያስበልጠው ወይም የሚያሳንሰው ነገር የለም። በተጨማሪ ደግሞ ግብረ-ሶዶሟዊነት እና የወሲብ አጥቂነትን ሚያገናኝ ምንም ነገር የለም። አንድ ሰው ገና ለገና ጌይ ስለሆነ በዚች ዓለም ላይ ያለ ወንድ በሙሉ (ዘር ፣ እድሜ ፣ ቀለም ፣ ቁመት ፣ ፀባይ ፣ ሐብት ፣ የትምህርት ደረጃ .... ወዘተ ሳይለይ) ይማርከዋል ማለት አይደለም (በወሲብ አይን ማየት ይቅርና)። 

5 - "ግብረ-ሶዶማዊነት የወሲብ እና የአይምሮ በሽታ ያስከትላል"
ማንኛውም የሆነ ልቅ ግብረ-ስጋ ግኑኝነት ያባላዘር በሽታ ሊያስከትል ይችላል። ሆኖም ጌይ ወንዶች በ ኤድስ እና በሌሎች የአባላዘር በሽታዎች የመጠቃት እድላቸው ከፍተኛ ነው።  ምክንያቱም ባዬሎጂ እንደሚያስረዳው የሰው ፊንጢጣ የተሰራው በጣም ስስ ከሆነ ቲሹ ሰለሆነ በቀላሉ ሊሰነጠቅ እና በሽታ ሊያስተላልፍ ይችላል። ግን ይህ ኮንዶም በመጠቀም በቀላሉ ሊውገድ ይችላል ። በኢትዮጵያ ውስጥ ትልቅ የኤድስ ወረርሽኝ አለ፤ በተለይ በጌይ ወንዶች መሐል። ተለያዩ ፀረ-ኤድስ አካሎች ቢኖሩም ጌይ ለሆኑ ሰዎች ምንም አይነት እርዳታ አይሰጡም። ይህም የሆነው ሐገሩ (መንግስት) በሚደግፈው ጥላቻ ምክንያት ነው። ስለዚህ ችግሩ በኢትዮጵያ ውስጥ በግብረ-ሶዶማውያን ላይ የሚያተኩር ጸረ ኤድስ እና ሌሎች የጤና ተቋሞች አለመኖር ነው እንጂ ግብረ-ሶዶማውያን ሰለሆኑ አይደለም።
አንድአንድ ጥናቶች እንደሚያሳዩት ብዝ ግብረ-ሶዶሜያውያን ከሌሎች ሰዎች የበለጠ ለእይምሮ በሽታ የመጋለጥ እድላቸው ከፍተኛ ነው። ይህም የሚከሰተው ከህብረተሰብ በሚመጣ ትልቅ ግለት እና ማንቋሸሽ ነው። አንድ ሰው በህይወት ዘመኑ በሙሉ ሲንቁአሸሽ ፣ ሲሰደብ ፣ ሲደበደብ ወዘተ በዓውምሮው ላይ ትልቅ ተጽአኖ ያመጣል። በተጨማሪ ደግሞ ሚሰማቸውን ስሜት ጨፍልቀው ፤ እንደሌላው ተመሳስለው ለመኖር ሲሞክሩ ወይም ደግሞ እውነተኛ ማንነታቸውን ደብቅው ሁለት ህይወት (Doubel life)  ለለመኖር ሲሞክሩ ፣ በጭንቀት እና ባለመረጋጋት አይምሮአቸውን ያሳብዳሉ። ነገሮች ካልተቀየሩላቸው ይህ ሁኔታ ወደ ባሰ የአይምሮበችምሽታ ወይም እራሳቸውን እንዲያጠፉ ይገፋፋቸዋል።

No comments:

Post a Comment